CERS-Bureau of Agriculture
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት የአስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን በወጣ አዋጅ ቁጥር 199/2015 መሠረት የግብርና ቢሮ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባራት ተሰጥተውታል፡፡
O የግብርና ልማትን ለማስፋፋት የግብርና እና የእንስሳት ግብዓቶችን ማባዣ፣ የዕፅዋት እና የእንስሳት ጥራት ቁጥጥር ማዕከላትን፣ ማሰልጠኛ ተቋማትንና ላቦራቶሪዎችን ያቋቁማል፣ ያስፋፋል፣
O በግብርና፣ በእንስሳትና በአሳ ልማት ኢንቨስትመንት ዘርፍ ለተሰማሩና ለሚሰማሩ ባለሀብቶች እና ባለድርሻ አካላት መረጃና የቴክኒክ ድጋፍ ያደርጋል፣
O የግብርናውንና የእንስሳት ዘርፍ ምርትና ምርታማነት ለማሻሻል ለአርሶ አደሩ፣ ለአርብቶ አደሩ እና ለግል ባለሀብቱ የሚሰጡ የኤክስቴንሽንና የሥልጠና አገልግሎቶች እንዲስፋፉ ያደርጋል፣
O የግብርና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠናው ኮሌጆችን ያስተዳድራል፣
O የግብርና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ከክልሉ የሰው ኃይል ፍላጎት ጋር መጣጣሙን ያረጋግጣል፣ ስልጠናው ፍላጎትን መሰረት ያደረገ እንዲሆን ያደርጋል፣
O የግብርና፣ የእንስሳት እና አሳ ግብዓት አቅርቦት፣ ስርጭትና ግብይት አቅምን ይገነባል፣ የብድር አቅርቦትና ስርጭት ያመቻቻል፣ ያረጋግጣል፣
O የግብርና፣ የእንስሳትና አሳ ምርት ግብዓት ወይም ግብዓት ብዜት ዘርፍ ለሚሰማሩ ድርጅቶች ወይም ግለሰቦች የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ይሰጣል፣ይቆጣጠራል፣ በሕግ መሰረት ይሰርዛል፣
O የግብርና፣ እንስሳትና አሣ ኤክስቴንሽን መርሃግብር ያዘጋጃል፣ ስትራቴጃዎችና ስልቶችን ይቀይሳል፣ ይተገብራል፣ የኤክስቴሽን ስርዓቱን በማጥናት እንዲሻሻል ያደርጋል፣
O አርሶ አደሮች በህብረት ስራ ማሕበራትና በግል ባለሀብቶች አማካይነት የሚካሄዱ የዘር ብዜት ስራዎች እንዲስፋፉ ያደርጋል፣ ያስተባብራል፣ የቴክኒክ ድጋፍና የምክር አገልግሎት ይሰጣል፣
O ሕገ-ወጥ የግብርና፣ የእንስሳትና የአሣ ግብዓቶች ግብይትና ዝውውር ይቆጣጠራል፣ ይከታተላል፣ በሕግ መሰረት እርምጃ ይወስዳል፣
O የግብርና፣ የእንስሳትና የዓሣ ልማት ባለሙያዎችን መልምሎ ያሰለጥናል፣ የአርሶ አደሮች የስልጠና ማዕከላትን ያቋቁማል፣ ያስተዳድራል፣
O ከአጎራባች ክልሎች ወደ ክልሉ የሚገቡ የእንስሳት፣ እፅዋት፣ የአዝርዕት እና ተዋፅኦ ላይ ተገቢውን ቁጥጥር ያድርጋል፣
O በክልሉ የሰብል ሃብት ላይ ወረርሽኝ እንዳይከሰት ይከላከላል፣ ከተከሰተም በአፋጣኝ በቁጥጥር ስር እንዲውል ያደርጋል፣
O በግብርና ምርት እና በእንስሳት ሃብት ላይ ተፅዕኖ የሚያስከትሉ ወቅታዊ ሁኔታዎችን ይከታተላል፣ የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ስርዓት ይዘረጋል፣ አፋጣኝ እርምጃ ይወስዳል፣
O የሰፈራ ፕሮግራም በበላይነት ይመራል፣ ሰፋሪው እስከሚቋቋም ድረስ አስፈላጊ የሆኑ የእርሻ መሳሪያዎች፣ ግብዓትና መሰረተ ልማቶች እንዲሟሉ ያደርጋል፣
O የግብርና ምርቶች ግብዓት እና የእንስሳት ሃብት ልማት አስፈላጊ መሰረተ-ልማቶች ይገነባል፣ እንዲገነቡና እንዲስፋፉ ያደርጋል፣
O የክልሉን አጠቃላይ የግብርና እና የእንስሳት ግብዐትና የአደጋ ቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃ ያሰባስባል፣ ያጠናቅራል፣ይተነትናል ለሚመለከታቸው አካላት ያሰራጫል'
O ግብርና፣ የእንስሳትና የአሣ ሃብት ምርምር ዓቅም ይገነባል፣ የምርምር ውጤቶችን ያሰርፃል፣ የምርምር ባለድርሻ አካላት በቅንጅትና በትብብር የሚሰሩበትን ስርዓት ይዘረጋል፣
O የሰብል ሃብት ልማት እንዲስፋፋ ያደርጋል፣ ተስማሚ ፖኬጆችን ያዘጋጃል፣ ተግባራዊ ያደርጋል፣
O የግብርና ምርት፣ የእንስሳትና ዓሣ ልማት ግብዓት ጥራት አጠባበቅ ለአምራቾችና ለሌሎች ተዋንያን የምርምር አገልግሎትና ስልጠና ይሰጣል፣ የግብዓቶች ጥራት ቁጥጥር ያደርጋል፤
O በክልሉ በሰው ሰራሽ ወይም በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት የተፈናቀሉ ወገኖችን በቋሚነት መልሶ ለማቋቋም የሚረዱ የመልሶ ማቋቋሚያ ፕሮጀክቶች አጥንቶ ያቀርባል፣ ሲጸቀድም ተግባራዊ ያደርጋል፣
O በዕለት ዕርዳታ ስራ ላይ ከሚንሳቀሳቀሱ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በጋራ ይሰራል፣ አሰራራቸውን በበላይነት ይመራል፣ ይቆጣጠራል፣
O የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ስራዎችን ያከናውናል፣
O በገጠር ለምግብ ዋስትና ችግር የተጋለጡ አካባቢዎችንና የኀብረተሰብ ክፍሎችን ይለያል፣ መንስኤውን ያጠናል፣ ይደግፋል፣ በዘርፉ የሚሠሩ ባለድርሻ አካላትን ያስተባብራል፣
O ዘላቂ የግብርና ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችል የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ስራዎች ያከናውናል፣ ያስተባብራል፣ ይመራል፣
O የጥቃቅንና የአነስተኛ መስኖ ልማት እንዲስፋፉ አግባብ ካለው አካል የተጠኑ ጥናትና ዲዛይን መሰረት በማድረግ ግንባታ እንዲካሄድ ያደርጋል፣ አቅርቦቱንም ይደግፋል፣
O የግብርና ምርምር አቅም ይገነባል፣ ባለድርሻ አካላት በቅንጅትና በትብብር የሚሰሩበትን ስርዓት ይዘረጋል፣
O የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ዘርፍ ምርትና ምርታማነት ለማሻሻል የእንስሳትና ዓሳ ዝርያ ብዜት ስርዓት ይዘረጋል፣ ይተገብራል፣ አገልግሎቶች ይሰጣል፤ እንዲስፋፉ ያደርጋል፤
O የእንስሳት ክትባትና መድሐኒት አቅርቦት፣ ግብይት፣ አያያዝ ዝውውር ስርዓት ይዘረጋል፣ የብቃት ማረጋገጫ ይሠጣል፣ ይቆጣጠራል፣ በህግ መሠረት እርምጃ ይወስዳል፣
O የእንስሳት ገበያና የዝውውር መስመሮችን ይወስናል፣ ይቆጣጠራል፣ የኳራንቲይን አገልግሎት ይሰጣል፣ ከአጎራባች ክልሎችና ከፌዴራል መንግሥት አካላት ጋር በቅንጅትና ትብብር ይሠራል፣
O የእንስሣት በሽታ ወረርሽኝና ተዛማች በሽታዎች እና የውሃ አካላት ብክለት የመከላከያና የመቆጣጠሪያ ሥርዓት ይዘረጋል፣ ያስፈጽማል፣ ሲከሰትም አፋጣኝ እርምጃ ይወሰዳል፣
O የእንስሳት የጤና አገልግሎት ይሰጣል፣ የእንስሳት በሽታዎች ምርመራ፣ አሰሳና ቁጥጥር ሥራዎችን ያካሄዳል፣
O የእንስሳትና ዓሳ ሀብት በልማት ቀጠናዎች ይለያል፣ እንዲለማ ተገቢውን ድጋፍ ያደረጋል፣
O በክልሉ ለሚገኙ ቄራዎችና የእርድ ቦታዎች የቁም እንስሳትና የበድን ስጋ ምርመራና ቁጥጥር ያደርጋል፣ መስፈርቶችን ያዘጋጃል፣ ተግባራዊነታቸውን ይቆጣጠራል፣ ባለሙያ ይመድባል፣ ደረጃቸውን ያልጠበቁትን ይዘጋል፣ አስፈላጊ እርምጃ በሚመለከተው አካል እንዲወሰድ ያደርጋል፣
O ዓላማውን ለማሳካት የሚረዱ ሌሎች ተግባራትን ያከናውናል፡፡
Copyrights 2025. . Centeral Ethiopia Bureau of Agriculture. All Rights Reserved.
Developed by CE-SCIENCE AND INFORMATION TECHNOLOGY BUREAU