• Call Us
  • +25146 554 16 87

የ 5 በ 5 የከተማ ግብርና ፕሮጀክት

                        የ5 5 የከተማ ግብርና ፕሮጀክት (5 የአትክልት አይነት በቤተሰብ)

ይህ ፕሮጀክት ‘’ምግቤን ከጓሮዬየሚል ስያሜ የተሰጠው ነው። ይህ ፕሮጀክት በከተማ የሚኖር ሁሉም ነዋሪ ቪላ ይሁን ፎቅ ላይ የሚኖር እያንዳንዱ ነዋሪ ቢያንስ 5 የአትክልት አይነት ይኖረዋል። ከእያንዳንዱ አትክልት 5 (አምስት) ፍሬ ያለማል ማለት ነው። በዚህ መሰረት በአንድ ቤተሰብ ግቢ ወይም መኖሪያ አካባቢ በትንሹ ሀያ አምስት አትክልቶችን ያለማል ማለት ነው። ይህ ኢኒሺዬቲቭግብርና የገጠር ስራ ነውየሚለው የተለመደዉ አስተሳሰብ መቀየር ያስቻለም ስልት ነው፡፡ በአሁኑ ዓመትም አዳዲስ የከተማ ግብርና ሥፍራዎችን የተጀመሩ ሲሆን እንደ ቲማቲም፣ ጎመን፣ ሰላጣ፣ ካሮት፣ ወዘተ በግቢዎቻቸው ባሉ ክፍት ቦታዎች፣ በቤታቸዉ ዙርያና በአጥር ግድግዳ በባልዲ ላይ ጭምር አትክልት በማምረት ከራሳቸዉ ፍጆታ አልፈዉ ለሽያጭም የሚያቀርቡ የከተማ ነዋሪዎች ብቅ እያሉ ነዉ።