• Call Us
  • +25146 554 16 87

5-10-25 የዶሮ ልማት ፕሮጀክት

                                                   5-10-25 የዶሮ ልማት ፕሮጀክት (ያልተደረሱትን መድረስ)

በገጠርም ሆነ በከተማ የተሻሻለ ዝርያ ዶሮ የሌለው ቤተሰብ አይኖርም በሚል እሳቤ፤ ለአንድ ዝቅተኛ ገቢ ላለው ቤተሰብ ቢያንስ 5 ዶሮ፤ ትንሽ ሻል ላለው 10 ከፍ ላለው ደግሞ 25 ዶሮዎች እንዲኖሩት ይሰራል የሚል ኢኒሼቲቭ ነው። የኢኒሼቲቩ መነሻ የብልፅግናን አካታችነት በተግባር ለማረጋገጥ አጋዥ አቅም መሆኑን ማሳያ ነው። 25 በላይ የተሻለ የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ ያሉ ሁሉ ሊሰሩት የሚችሉት ስለሆነ አቅም የሌላቸው እንዳይገለሉ ያደርጋል። በዚህ መሰረት ከፍተኛ የመልማት አቅም ያላቸውን ወረዳዎች፣ ቀበሌዎችንና መንደሮችን በመምረጥ በዶሮ ልማት መንደር በማደራጀት የአርሶ አደሮችን የሴቶችንና ወጣቶችን ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ 51025 ዶሮዎችን በኩታ ገጠም ማርባት የተጀመረ ሲሆን እስካሁን 278 መንደሮች እንዲሁም በከተማ ዘመናዊ የዶሮ እርባታ አሰራር 5 ከተሞች ስኬታማ ስራ ተሰርቷል፡፡ ይህ ፕሮጀክት የብዙ አቅመ ደካማ ቤተሰቦችን ቀልብ ስቧል፣ተጠቃሚም ሆነዋል።