• Call Us
  • +25146 554 16 87

የግብርና ግብዐት አቅርቦትና ገጠር ፋይናንስ ዘርፍ

                                 የግብዓት አቅርቦት ዘርፍ ተጠሪነቱ ለግብርና ቢሮ ሆኖ የሚከተሉት ተግባርና ኃላፊነት ይኖሩታል፤

O የግብዓት አቅርቦት ስርዓት ክትትል በማድረግ እና ግብይት ስርዓት ፖሊሲዎችንና ፕሮግራሞችን በጥናት ላይ ተመስርቶ ይቀርጻል፣ ውሳኔ ሲያገኝ ተግባራዊ   ያደርጋል፤

O የግብዓት አቅርቦቱ ለአርሶ አደሩ በመጠን፣ በጥራትና በዓይነት ተደራሽ እንዲሆን ጥናት ያደርጋል፤

O በግዥ የሚቀርቡ ግብዓት እና ስርጭት ተግባር ላይ የተሳተፉ እና ለመሳተፍ የሚፈልጉ አካላትን የአቅም ግንባታ ስራ ይሰራል፤

O ጥራትና ደረጃው የተጠበቀ ግብዓት ለአርሶ አደሩና፣ ለባለሀብቶችና የተደራጁ የማህበረሰብ አካላት እየቀረበ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ ይከታተላል ችግር ያለባቸውን O በመለየት ለበለጠ ሙያዊ ጥራት ቁጥጥር ለሚመለከታቸው ላቦራቶሪ እንዲያሳወቁ ያደርጋል አፈጻጸሙን ይከታተላል፣

O የግብዓት አመራረት፣ ክምችት፣ የአጓጓዝ ሂደት በሥርዓት እንዲመራ የአሰራር ሥርዓት እንዲዘረጋ ያደርጋል ፡፡

O ከምርምር ማዕከላትና ከግብዓት አቅራቢ ማዕከላት ጋር የቅርብ ግንኙነት በመፍጠር ተፈላጊ የስነ- ህይወታዊ ግብዓት ምርት ግብዓት ውጤታማ የሆኑ በምርምርና   በጥናት እንዲቀርቡ በቅንጅት ይሰራል ፣

O ለምርምር በሚቀርቡ ሃሣቦች/ የምርምር ኘሮፖዛሎች/ ላይ በሚደረግ ውይይት በመሳተፍ የበኩሉን አስተያየት ያቀርባል፣

O የግብዓት ጋር የተገናኙ የልማት ፕሮጀክቶችን ያዘጋጃል፣ ያፀድቃል፣ አተገባበራቸውንም በመከታተል ሪፖርት ያቀርባል፣

O በግዥ የሚቀርቡ ግብዓቶች ፍላጎት ትንበያ፣ እና ስርጭት ዙሪያ ለአቅራቢዎች እና ተጠቃሚዎች ምቹ እንዲሆን አዳዲስ የአሰራር ሥርዓት ስለሚሻሻልበት ሁኔታ   ሀሳቦችን ያቀርባል፤ይዘረጋል፡፡

O በግብዓት ሥርጭት ዙሪያ ከተለያዩ አካባቢዎች የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዲስፋፋ ያደርጋል፤

O ቅንጅታዊ አሠራር ለማጎልበትና ለማጠናከር የሚያስችሉ ስልቶችን በመቀየስ በወቅቱ ግብዓት ለአርሶ አደሩ/አርብቶ አደሩ እንዲደርስ ያደርጋል፤

O ኅብረት ሥራ ማኅበራት፣ መንግስታዊ የልማት ድርጅቶችና ልማታዊ ባለሀብቶች በግዥ የሚቀርቡ ግብዓቶችና ሥርጭት ላይ እንዲሳተፉ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፤

O ግብዓቶች ተገዝተው ከመቅረባቸው በፊት ተገልጋዮች ዝግጅት እንዲሁም የቅበላ አቅም በመገምገም ዝግጁ እንዲሆኑ ያደርጋል፣ የዝግጅት ክፍተት ሲኖር የማሟያ   ስልት ይነድፋል፣

O በአከባቢው የሚተገበሩ የተፋሰስ ልማትና ከሌሎች የግብርና ልማት ሥራዎች ጋር በተቀናጀ መልኩ የግብርና ግብዓት እና ስርጭት ለማስፋፋት የሚያስችሉ አዳዲስ የውጤቶችና የተሸሻሉ አሰራሮች በማሰባሰብ ለቴክኒክ አሰራር ዝግጅት ግብዓት ደርጋል፤

O ተገቢ የግብርና ሜካናይዜሽን ምንጮችን የግዥ ስልት፣ እቅድ ፣ፖሊሲ፣ አሰራርና፣ መመረያዎችን መፈተሽና ተግባራዊነታቸውን ይከታተላል፤

O የግብርና ሜካናይዜሽን ከጠቅላላው የግብዓት ስልት አንጻር በመቅረጽ ይመራል፤

O ግዥ፣ ማከማቸትና ማሰራጨት የሥራ እንቅስቃሴዎች የጥራትና ብቃት፣ የዋጋ ተወዳዳሪነት እንዲሁም የላቀ አገልግሎት ለውስጥና ለውጭ ተገልጋዮች ከመስጠት   አንጻር ያለውን እንቅስቃሴ በመፈተሽ አፈፃፀሙን ይከታተላል፤

O የተፋሰስ ልማት በሚካሄድበት አከባቢ የሜካናይዜሽን ግብዓት ሥራዎች ያሉበትን ደረጃና ችግሮችን ለመፍታት ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት መነሻ የሚሆኑ     መረጃዎችን በማሰባሰብ፣ ይለያል፤

O የሜካናይዜሽን ግብዓት መረጃዎችን የማደራጀት፣ ለዘመናዊ መረጃ ቋትና ፣ለዕቅድ ዝግጀት ያመቻቻል፤

O የሜካናይዜሽን ግብዓት ሥራ በአከባቢው ያለበትን ደረጃና የህበረተሰቡን ልማዳዊ አሠራር በመለየት የተሰበሰቡ መረጃዎችን መሠረት በማድረግ ትንታኔ መስጠት፣   በአግባቡ ያደራጃል፤

O በአከባቢው የሚተገበሩ የተፋሰስ ልማትና ከሌሎች የግብርና ልማት ሥራዎች ጋር በተቀናጀ መልኩ የሜካናይዜሽን ግብዓት ለማስፋፋት የሚያስችሉ አዳዲስ   ውጤቶችና የተሸሻሉ አሰራሮች በማሰብሰብ ለቴክኒክ አሰራር ዝግጅት ግብዓት ያደርጋል፤

O የሜካናይዜሽን ግብዓት በተመለከተ ለሚዘጋጁ የአጭር ጊዜ ፕሮጀክቶች፣ አዳዲስ የአሰራር ስርዓቶችን፣ ህጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች መረጃዎችን ያሰባስባል፤

O የግብርና ሜካናይዜሽን ግብዓት በሚመለከት በተዘጋጀው የስልጠና ሰነድ መሰረት ለህብረተሰቡ የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና ይሰጣል፤

O በተፋሰስ ልማት ተግባራዊ የሚደረጉ የሜካናይዜሽን ግብዓት ሥራዎች በተዘጋጀው ዕቅድና መመሪያ መሰረት እንዲከናውኑ ሙያዊ ድጋፍ በመስጠት ይከታተላል፤

O ዘርፉ ከስሩ የሚከተሉት ዳይሬክቶሬቶችን  ያስተባብራል፡-

                        o. የግብርና ሜካናይዜሽን ዳይሬክቶሬት

                         o. ግብርና ግብአት አቅርቦት ዳይሬክቶሬት