CERS-Bureau of Agriculture
የ10ሜ በ10ሜ (100ካሜ) ቅመም ፕሮጀክት /(100 ካሜ ቅመማ ቅመም በቤተሰብ)/፡
30-40-30 ማሳ ውስጥ በትንሹ 100 ካሜ አንድ የቅመም አይነት ያለማል ማለት ነው። በተለይም ከፍተኛ ዋጋ የሚያወጡ የቅመም አይነቶች ላይ በልዩ ትኩረት ይሰራል ማለት ነው። በመሆኑም በፍራፍሬ መንደር ውስጥ የቅመማ ቅመም መንደር ይኖራል ማለት ነው። በዚህ የቅመማ ቅመም ልማት ኢኒሼቲቭ ፕሮጀክት ዙሪያ በተገኙ መድረኮች ሁሉ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ እየተከናወነ የቀጠለ ሲሆን በ2015/6 ብቻ 10በ10 እና 20በ20 የተለያዩ ቅመማ ቅመም ሰብሎች ልማትን በ28 ወረዳ፣ 120 ቀበሌ፣ 94 አማማ፣ 25 ት/ቤቶች፣ 7 የሃይማኖት ተቋማት፣ 3 የመንግስት ቡና ችግኝ ጣቢያዎች 175 ክለስተር 167,951 ካሜ ላይ 8,863 ወንድ፣ 7,439 ሴት በድምሩ 16,302 አርሶ አደሮች ሮዝመሪ፣ በሶቢላ፣ ጤናዳም፣ ነጭና ጥቁር አዝሙድ፣ ደምብላል፣ አብሽ፣ ኮሰረት፣ አሪቲ በማልማት ተጠቃሚ መሆን ችለዋል፡፡ ከሀገር ውሥጥ ገበያ ባሻገር ለውጭ ገበያ ጭምር በማቅረብ ህ/ሰባችንም ሀገራችንም ተጠቃሚ ማድረግ የቻለ ኢኒሺዬቲቭ ነው፡፡
Copyrights 2025. . Centeral Ethiopia Bureau of Agriculture. All Rights Reserved.
Developed by CE-SCIENCE AND INFORMATION TECHNOLOGY BUREAU