CERS-Bureau of Agriculture
የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም መሪ ሥራ አስፈጻሚ ተጠሪነቱ ለግብርና ቢሮ ሆኖ የሚከተሉት ተግባርና ኃላፊነት አለው፡-
O የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችሉ አዳዲስ የፖሊሲ ሃሳቦች፣ የህግ ማዕቀፎች፣ የሥራ መመሪያዎች፣ ማንዋሎች፣ የአሠራር ሥርዓቶች፣ በጥናት ተደግፈው እንዲወጡና እንዲሻሻሉ ይሠራል፣ ሲፀድቅም ተግባራዊ ያደርጋል፣ ውጤታማነታቸውን ይከታተላል፤
O የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ስራዎችን ውጤታማ የሚያደርጉ ስትራቴጂዎችን ተግባር ላይ እንዲውሉ ያደርጋል፤
O የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አሰራር በተመለከተ ምርጥ ተሞክሮዎችን እንዲቀሙሩና እንዲስፋፉ ያደርጋል።
O የመሬት መጠቀም መብት ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችሉ ጥናቶች እንዲካሄዱ ያደርጋል፤ የጥናት ውጤቱም ወደ ተግባር የሚለወጥበትን መንገድ ያመቻቻል፡፡
O የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አሰራርን እና የመሬት አጠቃቀም ፖሊሲና ፕላን ዝግጅቱንና አተገባበሩን የሚያግዝ ለባለሙያዎች፣ ባለድርሻ አካላትና ለማህበረሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እንዲከናወኑ ያደርጋል፤ የማስፈፀሚያ አቅምን በማደራጀት ተገቢ የማብቃት ሥራ እንዲከናወን ያደርጋል፤
O በክልል አቀፍ ደረጃ እያንዳንዱ ማሳ መሬት ለምን ዓላማ መዋል እንዳለበት እንዲጠና በማድረግ ቴክኒካል ሪፖርት ያቀርባል፤
O የክልሉን የእርሻ፣ የደን፣ የግጦሽ፣ የዉሃ አካላት፣ መሠረተ ልማቶች እና ለሌሎች የግንባታ ቦታ ሥርጭትና ጠቀሜታ እንዲጠና በማድረግ፤ ለመሬት አጠቃቀም ፕላን ዝግጅት ግብዓት እንዲሆኑ ያደርጋል፤
O የክልሉ የመሬት እምቅ ሀብት ደረጃ እንዲጠና በማድረግ የመሬት እንስሳትን የመሸከም አቅም ትንበያ ሥራ እንዲከናወን ያደርጋል፤
O ከዞን እስከ ቀበሌ የመሬት አጠቃቀም ሥርዓት ግንባታ እንዲዘረጋ እና የመሬት አጠቃቀም ፕላን ዝግጅት፣ ትግበራና ቁጥጥር ሥራዎችን ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል፤ O ከዞኖች ጋር ይሠራል፣ ሙያዊ እገዛ እንዲያገኙ ያደርጋል፤
O በተለያዩ የመሬት አጠቃቀም መካከል ግጭትና ሽሚያ ሲፈጠር በጥናት የተደገፈ የውሳኔ ሃሳብ በማዘጋጀት ለውሳኔ ሰጭ አካላት ያቀርባል፤
O በክልሉ ጎጂ የመሬት አጠቃቀም ላይ የቁጥጥር ተግባር ስለሚከናወንበት ሁኔታ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ስትራቴጂ ይቀይሳል፣ ቁጥጥር እንዲደረግም ያደርጋል፤
O ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላትና የተለያዩ ተቋማትን በመቀናጀት የአገሪቱን ስነ-ምህዳር ቀጠናዎች ክፍፍል እንዲዘጋጅ ያደርጋል፤
O ለየአካባቢው ተስማሚ የሆኑ አዳዲስ የጥናትና የምርምር ውጤቶችን ያካተተ የመሬት አጠቃቀም ፕላን ዝግጅት ፓኬጆችን እንዲዘጋጁና እንዲተገበሩ ያደርጋል፤ ወቅታዊ የመሬት አጠቃቀምና ሽፋን ካርታና ሰነድ እንዲዘጋጅ ያደርጋል፤
O የገጠር መሬት ይዞታ መብት፣ ክልከላና ኃላፊነት አመዘጋገብ ህግና ሥርዓቱን ተከትሎ እየተካሄደ ስለመሆኑ በክትትልና ድጋፍ እንዲረጋገጥ ያደርጋል/ ያረጋግጣል፤
O የካዳስተር መረጃ አሰባሰብ፣ አደረጃጀት ስርጭት እና የካዳስተር ካርታ አዘገጃጀት በስታንዳርዱ መሠረት መፈፀሙን ድጋፍና ክትትል እንዲረጋገጥ ያደርጋል /ያረጋግጣል፡፡
O ለካዳስተር ካርታ ግብዓት የሚሆን የኦርቶፎቶና የመስመራዊ ካርታ ዝግጅት ሂደትን ያስተባብራል ይመራል፤አፈጻጸሙንም ይከታተላል፤ ያረጋግጣል
O ከመስክና ከተለያዩ ምንጮች የሚሰበሰቡ መረጃዎችን የጂ.አይ.ኤስ ሶፍትዌር በመጠቀም ለህጋዊ ካደስተር ስርዓት ጥቅም ላይ የሚውሉበትን አግባብ ክለላዊ ስታንዳርድ መሠረት ስለመሆናቸው ይከታተላል፤
O የአየር ፎቶግራፍ/የሳተላይት ምሥሎችን እስታንዳርድ ያዘጋጃል፣ እንዲሁም የማስነሳትና ግዥ አፈፃፀሙን ሥራ ይመራል ያስተባብራል፤
O ለመሬት አጠቃቀም ፕላን ግብዓት የሚሆኑ ክልላዊ ደረጃ የተሰበሰቡ የጂኦ ስፓሻል መረጃዎች በየጊዜው ክትትልና ግምገማ በማድረግ ተገቢውን መረጃ መያዛቸውንና ደረጃቸውን (standard) ያረጋግጣል፣የመረጃ ሥርዓት ማደራጀትና ለባለድርሻ አካላት ተደራሽ ያደርጋል፤
O የመሬት ሀብት፣ የመሬት አጠቃቀም ፕላኖችን፣ የስነ-ምህዳር እና የመሬት አጠቃቀምና ሽፋን መረጃዎችን በዳታ ቤዝ እንዲደራጁ ያደርጋል፣ ለተጠቃሚዉ በወቅቱ እንዲሰራጩ ያደርጋል፤
O የመሬት ይዞታ መረጃዎችና እና ሌሎች የምዝገባ ቅጂዎችን ህጋዊ ለሆነ አካል የሚሰጥበትን ስርዓት ይዘረጋል፤ አፈጻጸሙን ይከታተላል፤ ይቆጣጠራል
O ለመብት ክልከላና ኃላፊነቶች የተዘጋጁት ክልላዊ የገጠር መሬት አስተዳደር መረጃ ስርዓት በአግባቡ የተከናወነባቸው ስለመሆኑ ይከታተላል፣ ችግር ሲያጋጥም መፍትሄ ይሰጣል፤
O የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ዳታ ቤዞች እንዲመሠረቱ ያደርጋል፣ አጠቃቀማቸውን ይከታተላል፣ ይገመግማል፣ የመረጃዎች ቅጂ /backup/ ፋይል በአግባቡና በሚፈለገው ደረጃ መያዛቸውና መጠበቃቸውን ይከታተላል፣
O ለሴክተሩ ባለሙያዎች፣ በየግብርና ለተሰማሩ ባለሀብቶችና ቡድኖች የአቅም ግንባታ ሥልጠና፣ ተከታታይ የሙያ ማሻሻያ ትምህርትና ሥልጠና ስትራቴጂ ይቀይሳል፣ ሲፈቀድም ተግባራዊ ያደርጋል፣ውጤቱንም ይገመግማል፣ ግብረ መልስ ይሰጣል::
Copyrights 2025. . Centeral Ethiopia Bureau of Agriculture. All Rights Reserved.
Developed by CE-SCIENCE AND INFORMATION TECHNOLOGY BUREAU