• Call Us
  • +25146 554 16 87

የ20-20-10 የእንሰት ተክል ፕሮጀክት (50 የእንሰት ተክል ለአንድ ቤተሰብ) ፕሮጀክት

                          የ20-20-10 የእንሰት ተክል ፕሮጀክት (50 የእንሰት ተክል ለአንድ ቤተሰብ) ፕሮጀክት፡

የእንሰት ችግኝ ብዜትና ስርጭት፣ የእንሰት በሽታ መከላከል፣ የእንሰት ድህረ-ምርት ቴክኖሎጂ አጠቃቀም እና ምርታማነትን ማሻሻልን ያካተተ የምረትና ምርታማነት ማሳደጊያ ስልት ነው፡፡ ይህ ኢኒሼቲቭ እንሰትን በክልላችንና በሀገራችን ከመጥፋት ወደ ማስፋፋት ለመቀየር እና ከእንሰት የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ፋይዳዎችን ክልላችንና ሀገራችን ማግኘት እንድትችል የሚረዳ ነው። በመሆኑም እንሰት የሚሰጠውን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ኢኮሎጂያዊ ጥቅሞችን ለማግኘት አንድ ቤተሰብ 50 -100 እንስት እንዲኖረው እየተሰራ ነው። የአፈፃፀም ስልቱም በሀምሳው ላይ ለመጀመር 20-20-10 በሚል የአፈፃፀም ስልት ተጀምሮ እያደገ እንዲሄድ ታቅዶ እየተተገበረ ያለ ኢኒሺዬቲቭ ነው። ይህ ማለት በመጀመሪያው አመት በትንሹ 20 የእንሰት ችግኝ፣ በሁተኛው አመት 20 እና በሶስተኛው አመት 10 የእንሰት ችግኝ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር እንዲተክል በማድረግ አቅም ያለው አርሶ አደር ግን በአንድ አመት 100 በላይም መትከል እንዲችል እየተደገፈ ነው። የእንሰት ፕሮጀክቱ ቅድሚያ ትኩረት አድርጎ የሚጀምረው ዝናብ አጠር በሆኑና ድርቅ በሚያጠቃቸው እና የምግብ ዋስትና ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራ ይሆናል። ከዚህ ቀጥሎ ወደ ደጋማው በማስፋፋት ይሰራል። የእንሰት ፕሮጀክቱ ትኩረት ተደርጎ የሚሰራው ልማቱን በማስፋፋት፣ ድህረ ምርቱ ቴክኖሎጂ ላይ በተለይም እንሰትን በዱቄት መልክ ወደ ገበያ ማስጋባት ብቻ ሳይሆን የቆጮ ዱቄት ኤክስፖርት ማድረግ ላይ በልዩ ትኩረት ይሰራል። በዚህ መሰረት 2015/6 ብቻ የእንሰት ማሳ ሽፋን ለማሳደግ በቁጥር 84,239,080 ችግኝ 33,693 / 478,676 (ወንድ 417,149 ሴት  61,527) /አደሮች ማሳ ተከላ ለማካሄድ የአ/አደር መነቃቃት ከመፍጠር አንፃር የዚህ ኢኒሺዬቲቭ ሚና የጎላ የነበረ ሲሆን በተመሳሳይ በሁሉም ክልሉ አካባቢዎች 2016/7 ተከለ የሚሆን አምቾ በአርሶ አደር ከሚለማው 1,552,003 አሚቾ በተጨማሪ በተቋማት ጭምር እንዲሰፋ በማድረግ 255,864 አሚቾ በድምሩ 1,807,863 አምቾ ቀበራ እንዲካሄድ በማድረግ  90,487,044  ችግኝ  እንዲዘጋጅ ከማድረግ አንፃር የዚህ ኢኒሺዬቲቭ ድርሻ ጉልህ አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡