CERS-Bureau of Agriculture
30-40-30 ፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት
የ30-40-30 የፍራፍሬ ፕሮጀክት ኣላማ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የበለጠ ለማስፋት ከመደበኛ የፍራፍሬ ተከላ በተጨማሪ የወረዳዎች/የቀበሌዎች የፍራፍሬ ፖቴንሻል መሰረት ልዩ ድጋፍ በማድረግ በአንድ አ/አ ጓሮ በመጀመሪያ አመት 30፣ በሁለተኛ አመት 40፣ በሶስተኛ አመት 30 በመትከል በአጠቃላይ በ3 ዓመት ውስጥ አንድ አ/አደር ቢያንስ 100 ፍራፍሬ ችግኝ እንዲተክል ድጋፍ የሚሰጥ ሲሆን በዚህ ፕሮጀክት የተመረጠ መንደር ቢያንስ 100 አ/አደሮች ተሳታፊ በማድረግ የሚተገበር ነው፡፡ በተመሳሳይ በእምነት ተቋማት እና በመንግስት ተቋማት ከ100 - 10,000 የፍራፍሬ ችግኞች በ3 አመት መትከልን ታሳቢ ያደረገ ሲሆን የተመረጡ ፍራፍሬ አይነቶችም መዝ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ እና አፕል ናቸው፡፡ ተግባሩ በሁለት አመት ውስጥ ውጤት የተመዘገበበት ኢንሺዬቲቭ ነው፡፡ በዚህ መሰረት በ2015/6 በመኸር ወቅት በ30-40-30 ፕሮጀክት በቁጥር 643,195 የፍራፍሬ ችግኝ በ1,056 ሄ/ር ማሳ ተከላ በማከናወን አስደናቂ ውጤት የተመዘገበበት ነው፡፡
Copyrights 2025. . Centeral Ethiopia Bureau of Agriculture. All Rights Reserved.
Developed by CE-SCIENCE AND INFORMATION TECHNOLOGY BUREAU