CERS-Bureau of Agriculture
የክልሉ ግብርና ሴክተር የ2017 1ኛ ሩብ ዓመት የዋና ዋና ተግባራት አፈጻጸም ግምገማ እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ተጠናቋል፡፡
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ኡስማን ሱሩር በመድረኩ ማጠቀለያ ላይ እንደገለጹት የሩብ ዓመቱ አፈጻጸም በግብርናዘርፍ ለማሳካት ያስቀመጥናቸው ግቦች ትክክለኛ ሀዲድ ላይ መሆናቸውን ያሳያል ብለዋል፡፡
ግብርናን አዘምነን የህብረተሰባችንን ተጠቃሚነት እናረጋግጠለን ብለን የጀመርነው ተስፋ ወደ ሚጨበት ተስፋ ብርሃን እየተቀየረ መሆኑን ያመላከቱት ቢሮ ኃላፊው ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን፣ገበያ ማረጋጋት፣ ለአምራች አርሶአደሮች የተሻለ ገቢ መፍጠር፣የሞቱና ከአገልግሎት ውጪ የሆኑ መሬቶች ወደ ምርታማት መቀየራቸውን እንዲሁም በሁለም መዋቅሮች የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባህል ተቀራራቢ እንዲሆን ከማድረግ አንጻር የተሻለ አፈጻጸም መኖሩን ገልጸዋል፡፡
በኢኒሼቲቮች ትግበራ የብሮው ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶች አይተኬ ሚና እየተጫወቱ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡
አቶ ኡስማን አያይዘውም በሩብ ዓመቱ በግብርናው ሴክተር በሁሉም የተሻለ ውጤት መመዝገቡን አብራርተው ለውጤቱም ከክልል እስከ ታችኘው መዋቅር ያለው አካል በተናበበ፣ በተቀናጀና በተባበረ ጥረት ነው ብለዋል፡፡
በሩብ ዓመቱ የተገኙ ስኬቶችን ማጽናትና ማነቆዎችን መፍታት ከሁሉም አካላት ይጠበቃል ያሉት አቶ ኡስማን ለዚህም ሁለችንም በተቀራራቢ የአስተሳሰብ ደረጃ ላይ መምጣት አለብን ብለዋል፡፡
በመድረኩም የሁሉም ዘርፎችና ተጠሪ ተቋማት የሩብ ዓመቱ ሪፖርት ቀርቦ ጥልቀት ያለው ውይይት ተደርጓል፡፡
የመድረኩ ተሳታፊዎች በሪፖርቶቹ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ክቡር አቶ ኡስማን ሱሩር ምላሽና ማብራሪያ በመስጠትና ቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል፡፡
Copyrights 2025. . Centeral Ethiopia Bureau of Agriculture. All Rights Reserved.
Developed by CE-SCIENCE AND INFORMATION TECHNOLOGY BUREAU