• Call Us
  • +25146 554 16 87

በቤተሰብ ደረጃ ድህነት በማሸነፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው- አቶ ኡስማን ሱሩር የካቲት 7/2017 ዓ.ም

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ግብርና ቢሮ 2017 የግማሽ ዓመት የዋና ዋና ግቦች አፈፃፀም ግምገማና የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በምክትል ርዕሰ-መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር የአስተሳሰብና የግንዛቤ ለውጥ በማጎልበት ድህነትን በቤተሰብ ደረጃ በማሸነፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

ለዚህም ግብርናን በማዘመን በትጋት ድህነትን ለማሸነፍ የግብርና ባለሙያዎች ሚናቸው ከፍተኛ እንደሆነ አብራርተዋል።

በዚሁም መሰረት ባለፉት ስድስት ወራት በግብርናው ዘርፍ ከዕቅድ ዝግጅት ጀምሮ የተቋሙን የማስፈጸም አቅም ግንባታ ለማሳደግ በቅንጅት በመሰራቱ በሁሉም ዘርፎች ለውጥ እየመጣ መሆኑን አስረድተዋል።

በተለይ ደግሞ ስድስቱን የግብርና ምሰሶዎች ለማሳካት በትኩረት በመሰራቱ ተጨባጭ ለውጥ እየመጣ ይገኛል ብለዋል።

ይህም ለቀጣይ ስራ የሚያነሳሳና ብርታት የሚሰጥ መሆኑን የገለፁት አቶ ኡስማን የታቀዱ ግቦች እንዲሳኩ ስራዎችን በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በዛሬው ውሎ በመድረኩ ላይ የክልሉ ግብርና ቢሮና የተጠሪ ተቋማት የስድስት ወራት አፈጻጸም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በነገው ዕለት ውይይት እንደሚካሄድ ተገልጿል።

በመድረኩ ላይ የክልሉ ግብርና ሴክተር የስራ ሀላፊዎች፣ የፕሮጀክትና ፕሮግራም አስተባባሪዎች እንዲሁም የሴክተሩ

ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።