• Call Us
  • +25146 554 16 87

የተቀናጀ ተተፋሰስ ልማት ንቅናቄዉ ግለቱን ጠብቆ እንዲቀጥል ማድረግ ያስፈልጋል:- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ዶ/ር

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው / የዘንድሮውን 2017 የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት አስመልክተው በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው የሚከተለውን መልዕክት አስተላልፈዋል።

የዘንድሮውን የተቀናጀ የበጋ የተፋሰስ ልማት ክልላዊ ንቅናቄ በይፋ ከጀመርን ወዲህ ፣ተግባሩን ለማሳካት በየአካባቢው እየታዪ ያሉት የህብረተሰብ ተሳትፎዎች አበረታች መሆኑን ገልፀዋል።

የተቀናጀ ተተፋሰስ ልማት ንቅናቄዉ ግለቱን ጠብቆ እንዲቀጥል ማድረግ እንደሚያስፈልግ የገለፁት ርዕስ መስተዳድሩ የሥነ አካላዊ ሥራዎችም ጥራታቸዉን የጠበቁና የአፈርና የዉኃ አካላትን ጤንነት በመጠበቅ ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻልና የአየር ንብረት ለዉጥን ለመከላከል የሚያግዙ እንዲሆኑ በትኩረት መሥራት ይጠበቃል