• Call Us
  • +25146 554 16 87

የቢሮ ኃላፊ መልዕክት

                                                   የተከበሩ አቶ ኡስማን ሱሩር

                            በምክትል ርዕሰ-መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት

                          ክላስተር አስተባባሪና  የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ መልዕክት

የተከበራችሁ የግብርና ቤተሰቦች!

ከሁሉ አስቀድሜ የክልላችንን የግብርና ልማት በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አገልግሎቶች ለመዘመንና በግብርና ልማት ምርታማነትን ለማፋጠን የሚስችል መረጃን ለሁሉም ተገልጋዮቻችን በሚገኙበት የዓለም ዳርቻ ሁሉ ተደራሽ ለማድረግ በሚያስችለን በዚህ ድረ-ገጽ ምረቃና ትውውቅ ዐውድ በመገኘታችሁ እንኳን ደህና መጣችሁ! በማለት የተሰማኝን ልባዊ ደስታ በክልሉ መንግሥት፣ በክልሉ የገጠር ልማት አካላትና በግብርና ቢሮ ስም ለመግለፅ እወዳለሁ፡፡

እንደሚታወቀው ዘመናችን የመረጃና መረጃም የዘመናችን ቁልፉና ዋነኛው የልማትና የብልፅግና ምንጭ ነው፡፡ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የሚጠቀመው የበይነ-መረብ አገልግሎትም በዓለማችንየህዝቦች መቀራረብን ብቻ ሳይሆን ጊዜን፣ ወጪንና ጉልበትን ከብክነት በመታደግ ኑሮን ከማዘመንና ከማቅለል ባሻገር በፈጣን የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት ልማትን በማፋጠን ብልፅግናን እንድንጎናፀፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡

                                  ተጨማሪ ያንብቡ